image
image
image
image
image

ባለፉት 6 ወራት ተግባራትን በተቀናጀና በተደራጀ መንገድ በመከወን ውጤታማ አፈፃፀም ማስመዝገቡን የልደታክ/ከተማ የመንግስት ንብረት አስተዳደር ጽ/ቤት ገለፀ።

የካቲት 5, 2018
ጽ/ቤት የ6ወር የእቅድ አፈፃፀም እና የተከለሰ የቀሪ 6 ወራት እቅድ ውይይት ከባለድርሻ አካላት ጋር አካሂዷል ። በውይይቱ ወቅት የጽ/ቤቱ ሀላፊ ኢንጅነር ቅድስት ማቲዎስ እንደገለፁት ባለፉት 6 ወራት ስታንዳርዳቸውን የጠበቁ የመንግስት ህንፃዎችን በማልማት ምቹ የስራ አካባቢ የመፍጠር እና የማስተዳደር ስራ መሰራት መቻሉን ገልፀዋል። ኃላፊዋ አክለውም ምቹ የስራ አካባቢ የፈጠሩ የመንግስት ተቋማትን በማሳደግ የዘመነና ከብክነት የፀዳ የመንግስት ንብረት አስተዳደር መፍጠር መቻሉንም ገልፀዋል። ውስን የሆነውን የህዝብ እና የመንግስት ሀብት ለታለመለት አላማ እንዲውል ለማስቻል እና የህንፃ አገልግሎት ስርአትን በማሻሻል ቀልጣፋ እና ውጤታማ የመረጃ አያያዝ እና የአገልግሎት አሰጣጥ ስርአት እንዲኖር ለማስቻል እየተሰራ ነው ብለዋል ኢንጅነር ቅድስት። በቀጣይ 6 ወራት ቀሪ እቅድን ለመፈፀም በተሻለ የስራ ተነሳሽነት የተቀመጡ ግቦችን ማሳካት ይገባል ብለዋል። የውይይቱም ተሳታፊዎች እንደገለፁት ፅ/ቤቱ ውስን የሆነውን ሀብት ከብክነት አድኖ ለታለመለት አላማ እንዲውልና ምቹ የስራ አካባቢ በመፍጠር ረገድ የሰራው ስራ የተሻለ መሆኑን ገልፀዋል።

መልዕክትዎን ይላኩ

ሌሎች ዜናዎች